ባህሬን እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ዛሬ በይፋ እስራኤልን እንደሀገር የተቀበሉበትን ፊርማ በኋይት ሀውስ አኑረዋል።

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትረምፕ በቤተመንግስታቸው ኋይት ሀውስ ሆነው ባህሬን እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ዛሬ በይፋ እስራኤልን እንደሀገር የተቀበሉበትን ፊርማ ሲፈረሙ ታዛቢ ሆነዋል ።

” ከብዙ አስርት አመታት ግጭትና ክፍፍል ዛሬ አዲስ የሰላም መንገድ ጀምረናል ሌሎች የቀጠናው ሀገራትም ተመሳሳይ ፊርማ ያኖራል ። እሱም በጣም ቅርብ ነው ” በማለት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትረምፕ የተናገሩ ሲሆን አምስት ተጨማሪ ሀገራት ከእስራኤል ጋር ለመስራት ተቃርበዋል ቢሉም ስማቸውን ግን አልጠቀሱም።
የእስራኤሉ ጠ/ ሚ ቢንጃሚን ኔታንያሁ ስምምነቱን “የአብርሀም ልጆችን ያቀራረበ ” በማለት አውድሰው ባህሬን እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ለእስራኤል እውቅነሰ ስለሰጡ አመስግነው ሌሎች አረበረ ሀገራትም ተመሳሳይ ነገር እንደሚያደርጉ ተስፋ አድርገዋል።

የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስት ሼኪ አብዱላሂ ቢን ዘይድ በበኩላቸው ” ዛሬ አዲስ ጅማሮ መስክረናል ይሄም ጅማሬ ለመካከለኛው ምስራቅ ሰላም ያመጣል ብለን ተስፋ እናደርጋለን ። ሰላም ደግሞ ትጋት እና ወኔ ይፈልጋል ” ብለዋል።
ባህሬን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አብዱለሰቲፍ ቢን ራሺድ አል ዛይኒ ደግሞ ” ለረጅም ግዜ መካከለኛው ምስራቅ የቅጭትና የጥርጣሬ ቦታ ነው ዛሬ ግን በዚህ ስምምነት ይሄን መቀየር እንደሚቻል አምኛለው ” ብለዋል።

ባህሬን እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ለእስራኤል እውቅና በመስጠት ግብፅና ዮርዳኖስን ተቀላቅለዋል ።
የንግድ እና የዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውን ከእስራኤል ጋር ሀ ብለው በመጀመር አጠናክረው ይገፉበታል ተብሎ ይጠበቃል ።ይሄ ጉዳይ ከፍልስጤም ፣ከኢራን እና ከቱርክ ጠንካራ ተቃውሞ ቢገጥመውም።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *