ከኮቫክስ የተገኘውና 20 በመቶ ለሚሆን የኢትዮጵያ ህዝብ የኮሮና ክትባት በቅርቡ ወደ አገር ውስጥ እንደሚመጣ የጤና ሚኒስትሯ አስታወቁ።ኮቫክስ የተሰኘው ዓለም አቀፍ ጥምረት ለደሃ አገሮች በዕርዳታ መልክ ለማቅረብ ካቀደው የኮሮና ቫይረስ መከላከያ ክትባት ውስጥ፣ ኢትዮጵያ እስከ 20 በመቶ የሚሆነውን ሕዝቧን ለመከተብ የሚያስችል የክትባት መጠን በጥቂት ወራት እንደምታገኝ የጤና ሚኒስትሯ ሊያ ታደሰ (ዶ/ር) ማስታወቃቸውን የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ገልጿል።