ሁዋዌ በኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽንና ቴክኖሎጂ ፈጠራና ክህሎት 1,000 ኢትዮጵያውያን ተማሪዎችን አወዳድሮ አሸናፊ ለሆኑ ተወዳዳሪዎች ሽልማት ሰጥቷል
የቻይና ግዙፉ ካምፓኒ ሁዋዌ ለሶስተኛ ግዜ በኢትዮጵያ ባዘጋጀውና 1,000 የሚሆኑ የሰባት ዩንቨርሰረቲ ተማሪዎች የተሳተፉበት በኔትወርክና በክላወድ ኔትወርክ ውድድር የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ 20 ተማሪዎችን ባለፈው ሀሙስ በኢሊሊ ኢንተርናሽናል ሆቴል በተካሄደ ፕሮግራም የተለያዩ የሁዋ ዌ ሽልማቶችን ሸልሟል።
አሸናፊዎቹ በአህጉር እና በአለም አቀፍ ደረጃ በሚደረጉ ተመሳሳይ የሁዋዌ ወድድሮች ላይም ይሸለማሉ ተብሏል።