ጠ/ሚ አብይ የአየር መንገድ የሰራተኛ ማህበር አመራሮችን ከታገዱበት ስራ እንዲመልሱ ተጠየቁ


የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኞች ዛሬ በፌስቡክና በቲዊተር ገፆቻቸው በጋሩት መልእከት ባቋቋሙት መሰረታዊ የሰራተኞች ማህበር ውስጥ ሲያገለግሉ የነበሩ አመራሮች በአየር መንገዱ የስራ ሀላፊዎች ያለ አግባብ ከስራ መታገዳቸውን ገልፀው የሀገሪቱን ጠ/ሚኒስትር አብይ አህመድን የታገዱትን ሰራተኞች ወደ ስራ እንዲመልሷቸው ጥሪ አቅርበዋል።


” የተከበሩ አብይ አህመድ ዛሬ የሰራተኞች ቀን ነው ።የእኛም ቀናችን ነው ።በዛሬው ቀን ለፍትህ ሲሉ ለእኛ ለተዋደቁና ከስራ የተባረሩ ሰራተኞች ድምፅ የምናሰማበት ነው።እርሶም አንደሚሰሙን ተስፋ እናደርጋለን በማለት ” በማህበራዊ ገፅ ላይ ፅፈዋል።

ከስራ ከታገዱት ውስጥ የማህበሩ ዋና ፀሀፊ ካፒቴን የሺዋስ ፈንታሁን ፣ምክትል ሀላፊ ማርቆስ ተሱወርቅ ፣ተከስተ ካሴ- ም/ፀሀፊ ፣ የማህበሩ ምክር ቤት አባል ሰምሀር አርአዶም ፣አልታሰብ ብርቁ-የማህበሩ ሒሳብ ሹም እንዲሁም ሀይለሚካኤል ዳመና የማህበሩ ኦዲተር ይገኙበታል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *