በንፋስ ስልክ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና በገርዢ የመኪና እና የሞተር መገጣጠሚያ ያለው ቶም የኤሌትሪክ ተሽከርካሪ በኤሌትሪክ የሚሰሩ ባይኮችን እየገጣጠምኩ ለገበያ ባቀርብም የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ከህግ አግባብ ውጪ ታርጋ የላቸውም በሚል ወደ 300 የሚሆኑ ደንበኞቼን ሳይክል አስሮብኛል ሲል ለፊደል ፖሰት ገልፇል።
ባይኮቹ በልዩ መለያ መስተናገድ አንደሚችሉ የትራንስፖርት ባለስልጣን ደብዳቤ ቢፅፍም ይሄን ወደ ጎን በመተው ባይኮቹን የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ እያሰረ መሆኑን የቶም የኤሌትሪክ ተሽከርካሪ አቶ በረከት ተስፋዬ ተናግረዋል።
” የኢትዮጵያን በካይ ጭስ ለመቀነስ አስበን ነው በኤሌትሪክ የሚሰሩ በይኮችን እያመረትን ያለነው። ነገር ግን ገጣጥመን ሳይሆን ሰርቀን ያመጣን ይመስል ትራንስፖርት ቢሮው ሳይክሎቹን እያሰረ ነው ።ታርጋ የለውም ይሉናል ነገር ግን ከትራንስፖርት ባለስልጣን ለኤሌክትሪክ ባይክ መመሪያ ስላልተዘጋጀ ያለታርጋ ማሽከርከር ይችላሉ የሚል ደብዳቤ የተፃፈልን ሲሆን ደርጅቱ ልዪ መለያ ስጥቷቸው ባይኮቹ በመንገድ ላይ እያሉ ነው የታሰሩት ።”
” ኢ-ባይክ በተሽከርካሪ በካይ ጭስ የሚደርሰውን የከባቢ አየር ብክለትን፣ የጤና ቀውስ ለመቀነስ፣ አነስተኛ ፍጥነት ስላላቸው የትራፊክ አደጋን ይቀንሳሉ ብለን የሰራነው ልንበረታታ ሲገባን የዚህ አይነት ነገር መፈጠሩ ያሳዝናል ።” ብለዋል።
የትራንስፖርት ባለስልጣን ችግሩን ለመቅረፍ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ ህግን የተከተለ አካሄድ አየሄደ መሆኑን ገልፆ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ጋር የመናበብ ችግር አንዳለ ገልፇል።